Tuesday, October 29, 2013

አስተውል!

የእግዜርን ስም ጠርቶ የለመነህን ሰው፣
እንዲሁ አትመልሰው፤
       ቢቻልህ መጽውተው፣
           ከራበው አጉርሰው፣
           ከራዘው አልብሰው፡፡
አደራ ተጠንቀቅ፡-
በአምላከክ ሥራ ገብተህ-
      እርሱን እንዳትወቅሰው፤
በክፉ ፊት ገርፈህ ለማኝ እንዳትለው፣
ክፉም ቃል ተናግረህ እንዳታሳዝነው፡፡
ከቶ አይኖርምና ወዶ የሚለምን፣
ፈጥነህ እንዳትስት አስተውል ዓለምን፡፡
ነገር ሲገላበጥ በፍትህ ጎዳና፣
ሲለ'መኑ ኖሮ መለመ'ን አለና፤
እግዜር ሲፈጥረንም፡-
አንዱን ለመለመን- ሌላውን ለመስጠት
                    ከቶ አይደለምና፡፡
እንዳገኙ መኖር ተደስቶ መሞት፣
እንደተለመኑ በክብር መሸኘት፤
      ትፈልግ ከሆነ የክብርን ገድል፣
      በተለመንህ ጊዜ በጥልቀት አስተውል፡፡

እምነት ያለ ሥራ ብቻውን ያድናልን???

መልካም ሥራ አያስፈልግም፣ ማመን ብቻ ያድናል የምትሉ እስኪ እነዚህን ጥቅሶች አንቡ፡፡ ጽድቅበእምነት ብቻ ቢሆን ኖሮ እነዚህ የእግዚአብሔር ቃላት ለምን በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ተጻፉ??? እውነት ነው የጽድቅ በር የተከፈተልንበጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ የጽድቃችን መሰረትም በሩም እርሱ ነው፡፡ ይህ ማለት ግን በማመን ብቻ መዳንእንደሚቻል ተደርጎ ሊወሰድ ኣይገባውም፡፡ መልካም ሥራ ካልሰራን የክርስቶስ መሆናችንስ በምን ይታወቃል፡፡ በማመናችን ብቻ ለእርሱልንሆን አንችልም፡፡ ማመን ብቻው አያድንም፡፡ መታመንን መጨመር አለብን፡፡ መታመን ማለት ደግሞ ላመኑት መገዛት፣ የታዘዙትን መፈጸምማለት ነው፡፡ ይኸውም የሚገለጸው በመልካም ሥራ ነው እንጅ አምናለሁ እያሉ በመናገር ብቻ አይደለም፡፡ ለማነኛውም የሚከተሉትን ጥቅሶችአንብቡና ፍረዱ፡፡ እምነት ብቻውን ቢያድን ኖሮ እነዚህ ለምን ተጻፉ???

የያዕቆብ መልእክት
14 
ትዕግሥትም ምንም የሚጎድላችሁ ሳይኖር ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን ይፈጽም።

125 

ነገር ግን ነጻ የሚያወጣውን ፍጹሙን ሕግ ተመልክቶ የሚጸናበት፥ ሥራንም የሚሠራ እንጂ ሰምቶ የሚረሳ ያልሆነው፥ በሥራው የተባረከ ይሆናል።