የእግዜርን ስም ጠርቶ የለመነህን ሰው፣
እንዲሁ አትመልሰው፤
ቢቻልህ መጽውተው፣
ከራበው አጉርሰው፣
ከራዘው አልብሰው፡፡
አደራ ተጠንቀቅ፡-
በአምላከክ ሥራ ገብተህ-
እርሱን እንዳትወቅሰው፤
በክፉ ፊት ገርፈህ ለማኝ እንዳትለው፣
ክፉም ቃል ተናግረህ እንዳታሳዝነው፡፡
ከቶ አይኖርምና ወዶ የሚለምን፣
ፈጥነህ እንዳትስት አስተውል ዓለምን፡፡
ነገር ሲገላበጥ በፍትህ ጎዳና፣
ሲለ'መኑ ኖሮ መለመ'ን አለና፤
እግዜር ሲፈጥረንም፡-
አንዱን ለመለመን- ሌላውን ለመስጠት
ከቶ አይደለምና፡፡
እንዳገኙ መኖር ተደስቶ መሞት፣
እንደተለመኑ በክብር መሸኘት፤
ትፈልግ ከሆነ የክብርን ገድል፣
በተለመንህ ጊዜ በጥልቀት አስተውል፡፡
እንዲሁ አትመልሰው፤
ቢቻልህ መጽውተው፣
ከራበው አጉርሰው፣
ከራዘው አልብሰው፡፡
አደራ ተጠንቀቅ፡-
በአምላከክ ሥራ ገብተህ-
እርሱን እንዳትወቅሰው፤
በክፉ ፊት ገርፈህ ለማኝ እንዳትለው፣
ክፉም ቃል ተናግረህ እንዳታሳዝነው፡፡
ከቶ አይኖርምና ወዶ የሚለምን፣
ፈጥነህ እንዳትስት አስተውል ዓለምን፡፡
ነገር ሲገላበጥ በፍትህ ጎዳና፣
ሲለ'መኑ ኖሮ መለመ'ን አለና፤
እግዜር ሲፈጥረንም፡-
አንዱን ለመለመን- ሌላውን ለመስጠት
ከቶ አይደለምና፡፡
እንዳገኙ መኖር ተደስቶ መሞት፣
እንደተለመኑ በክብር መሸኘት፤
ትፈልግ ከሆነ የክብርን ገድል፣
በተለመንህ ጊዜ በጥልቀት አስተውል፡፡