Tuesday, October 29, 2013

አስተውል!

የእግዜርን ስም ጠርቶ የለመነህን ሰው፣
እንዲሁ አትመልሰው፤
       ቢቻልህ መጽውተው፣
           ከራበው አጉርሰው፣
           ከራዘው አልብሰው፡፡
አደራ ተጠንቀቅ፡-
በአምላከክ ሥራ ገብተህ-
      እርሱን እንዳትወቅሰው፤
በክፉ ፊት ገርፈህ ለማኝ እንዳትለው፣
ክፉም ቃል ተናግረህ እንዳታሳዝነው፡፡
ከቶ አይኖርምና ወዶ የሚለምን፣
ፈጥነህ እንዳትስት አስተውል ዓለምን፡፡
ነገር ሲገላበጥ በፍትህ ጎዳና፣
ሲለ'መኑ ኖሮ መለመ'ን አለና፤
እግዜር ሲፈጥረንም፡-
አንዱን ለመለመን- ሌላውን ለመስጠት
                    ከቶ አይደለምና፡፡
እንዳገኙ መኖር ተደስቶ መሞት፣
እንደተለመኑ በክብር መሸኘት፤
      ትፈልግ ከሆነ የክብርን ገድል፣
      በተለመንህ ጊዜ በጥልቀት አስተውል፡፡

No comments: