...
በቤትህ ላስቀድስ ስገኝ...
"ስግዱ" ይላል ዲያቆኑ - ራሱም እየተንበረከከ
"ቅድሜከ እግዚኦ ንሰግድ ወንሰብሐከ"
ይመልሳል ምዕመኑ - በተግባር እየገለጠ
መሬታዊ ጉልበቱን - ለፈጣሪው እየሰጠ...
...
የእኔ ልብ ግን ጠማማው - ፖለቲካዋን ጨማምሮ
ብሶቱን ለአምላኩ ይጮሃል - በስንኝ ነገር ቋጥሮ
...
<<አምላክ እንኳንስ ላንተ - በፍቅርህ ለምትገዛ
በባለጊዜ ወጠምሻ - ጉልበቴ በጽኑ ተይዛ
መንበርከክን ለምዳለች - መስገድ አይደለም ብርቋ
ባይሆን ለኋላ ርስቷ - ለሰማያዊ ጽድቋ
የአምልኮ ስግደቴን ተቀበል - ከመሬታዊው ለይና
ሥጋዬን ቢገዟትም - ነፍሴ በተስፋ ትጽና!>>
...
(መላኩ - መስከረም 30/2008)