አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር- አዲስ ነገር እናስባለን
አዲስ ቃልም እንገባለን፣
ይህንን ራእይ ሰንቀን- ይሄኛውን ደግሞ አቅደን
ያኛውንም እናልማለን፣
ግን ቃል በገባን ቁጥር- ፈፅመነው እናውቃለን?
በምንስ እንለካዋለን?
የራእያችንን መሳካት- የዕቅዳችንን ግብ መምታት
እንዴት ነው የምንለካው?
ለተፈጠርንበት ዓላማ- ለመኖር ላለመኖራችን
መመዘኛችን ምንድነው?
ከተፈጠርን ጀምሮ- በዚህች ምድር እየኖርን
ብዙ ነገር አሳልፈናል፣
ለርሀባችን መታገስ- ለገላችንም ልብስ መልበስ
ብዙ ወጥተን ወርደናል፣
ለእዕምሯችንም ምግብ- ሥጋዊ ዕውቀትን ፍለጋ
ብዙ ዘመናት ደክመናል፡፡
ነገር ግን ምንም እንኳን- ለኑሯችን ስንደክም
ዘመናችንን ብንጨርስም፣
በዓለም እርካታ የለምና- አሁንም በቃን አላልንም
ጎደሏችንን አልሞላንም፡፡
ታዲያ ለሥጋዊ ሕይወት ብቻ- እስከመቼ እንደክማልን?
ከመነንፈሳዊነት ርቀን፣
መቼስ ይሆን የምንኖረው?-በመንፈሳዊ ሕይወት
ወደ ሰማየ ሰማያት መጥቀን፡፡
መቼስ ይሆን የምንከተለው?-የአባቶቻችንን መንገድ
አገልግሎታቸውን ማን ያሳየን?
መንፈሳችንን ምን ሰለበው- ከሰማያዊት ጥሪ
ከቅዱሳን ሕብረት ማን ለየን?
የመንፈስ ልዕልናችንቀርቶ- ድክመታችንን ተመልክቶ
ዓለምስ ስለምን ይሳለቅ?
አጋንንት እንዴት ይበርታብን?-በመናፍቃን ማታለል
አማኝ እስከመቼ ይነጠቅ?
በመንፈስ ባዶ እየሆንን- እስከመቼ አንገት እንድፋ
እንዴት ዓለማውያንስ ይናቁን?
እስኪ በአባቶች ወኔ- ለጽድቅ በእውነት እንታጠቅ
ማንንነታችንን ይወቁን፡፡
እስኪ ደግሞ በዚህ ዓመት- ቃላችን በመንፈስ እናድስ
ቤተ ክርስቲያንን እናስባት፣
ፈተናዋ በዝቷልና- ልጆቿ ዓለማዊ ሆነን
መንፈሳችንም ዝሎባት፣
አጽራረ ቤተ ክርስቲያን- እንደ አሸን ፈልተዋልና
የዘመኑ ፍጻሜ ደርሶባት፡፡
እስኪ ሁላችንም ባንድ መንፈስ- ቃላችንን እናድስና
እናታችንን ደስ ይበላት፣
እኔ ግን ይሄው ለራሴ- ቃሌን እንደዚህ አድሻለሁ
የድርሻዬን ልወጣላት፡፡
ባለፀጋዋ እናቴ- አንቺ ስንዱ እመቤት ሆይ!
ሠላም ይሁን ለሁለንተናሽ፣
የፍቅርሽ ስፋት ጥልቀት- ለኔ ያደረግሽው ሁሉ
ገረመኝ እናትነትሽ፡፡
በዓለም ከወለደችኝ- ከሥጋዊቷ እናቴ
የአንቺ ፍቅር ይለያል፣
በረቀቀው ምሥጢርሽ- በግብረ መንፈስ ቅዱስ
ዳግም ልደቴን ሰጥተሽኛል፡፡
በልዩ እንክብካቤሽ- በመላዕክት ጠባቂነት
በቅዱሳንሽ ጸሎት፣
በያሬዳዊ ዜማሽ- በቅኔ በማኅሌቱ
በሰማያዊ ሥርዓት፡፡
ትህትናን በተመላ- የካህናት የሊቃውንት
የመምህራን አስተምህሮ፣
በአ-ቡ-ጊ-ዳ በአንቺው ጥበብ- በገበታ ፊደልሽ
አንደበቴ ፊደል ቆጥሮ፡፡
በውዳሴ ማርያም ዜማ- በድጓ በጾመ ድጓሽ
ከመላእክት ጋር ዘምሬ፣
ኪዳኑን አስደርሼ- ቅዳሴውን አስቀድሼ
በሥጋ ወደሙ ከብሬ፡፡
በብራና ላይ ጽሑፍሽ- በግድግዳ ላይ ሥዕልሽ
ጥበብሽን አይቻለሁ፣
በፍልፍል አብያትሽ- በረቀቁ ህንፃዎችሽ
ማንነትሽን አውቄአለሁ፣
ጠበልሽን ጠጥቼ- እምነትሽን ተቀብቼ
ተአምርሽን አድንቄአለሁ፡፡
የመጻሕፍትሽን ምሥጢር- የገድል የድርሳናቱን
የቅዱሳንን ማንነት፣
ለአንቺ ህልውና ሲሉ- የተቀበሉትን መከራ
የከፈሉትን ሰማዕትነት፡፡
የአባቶችን ልዩ ጥበብ- እንዴት ቅርሶችሽን ጠብቀው
ለእኔ እንዳደረሱልኝ፣
ትውፊትሽን ለማቆየት- አንችን ለእኔ ለማስረከብ
መስዋዕትነት ሲከፍሉልኝ፡፡
መከራ ስደታቸውን- ርሀብ ጥማታቸውን
በዓይነ ህሌናዬ አይቻለሁ፣
ፍቅር ፅናታቸው አስደንቆኝ- እነባቸውን አንብቻለሁ
ርሀባቸውን ተርቤአለሁ፡፡
እናም ይኸው እናታለም- ምንም አንቺን ለመረከብ
ማንነቴ ባይፈቅድልኝም፣
የእምነት የእውቀት ጉድለቴ- የልቤ አመንዝራነት
ባዶነቴ ቢያስጨንቀኝም፡፡
ከእኔ የአዕምሮ መርከስ- ከሐጢአት ከጉድፈቴ
የአንቺ ፍቅር ይበልጣልና፣
ይኸው ተረክቤሻለሁ፡-
የጻድቃን የሰማዕታትን- የቅዱሳን መላእክትን
ተራዳኢት አምናለሁና፡፡
እናም ከዛሬ ጀምሮ- ይኸው ቃሌን ሰጥቻለሁ
ተንበርክኬ ከእግርሽ ስር፣
ማንነትሽን ባላሳውቅ- ታሪክሽን ለዓለም ሁሉ
ያለ ፍርሃት ባልመሰክር፣
ትውፊትሽን ባላስጠበብቅ- የአምልኮና የዜማ
ሥርዓትሽን ባላስከብር፤
ምሥጢራትሽን አመሥጥሬ- ንዋያትሽን ደርድሬ
ከፍ ከፍ ባላደርግሽ፣
ልጆችሽም ይበዙ ዘንድ- ለሰማያዊ መንግሥት ጥሪ
ወንጌልሽን ባልሰብክልሽ፤
ይኸው በዳዊት መሐላ- እየማልሁ ከደጅሽ ልውደቅ፣
“ቤተ ክርስቲያን ሆይ!- ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ
ባላስብሽም ምላሴ- ከጉሮሮዬ ትጣበቅ፡፡”
አዲስ ቃልም እንገባለን፣
ይህንን ራእይ ሰንቀን- ይሄኛውን ደግሞ አቅደን
ያኛውንም እናልማለን፣
ግን ቃል በገባን ቁጥር- ፈፅመነው እናውቃለን?
በምንስ እንለካዋለን?
የራእያችንን መሳካት- የዕቅዳችንን ግብ መምታት
እንዴት ነው የምንለካው?
ለተፈጠርንበት ዓላማ- ለመኖር ላለመኖራችን
መመዘኛችን ምንድነው?
ከተፈጠርን ጀምሮ- በዚህች ምድር እየኖርን
ብዙ ነገር አሳልፈናል፣
ለርሀባችን መታገስ- ለገላችንም ልብስ መልበስ
ብዙ ወጥተን ወርደናል፣
ለእዕምሯችንም ምግብ- ሥጋዊ ዕውቀትን ፍለጋ
ብዙ ዘመናት ደክመናል፡፡
ነገር ግን ምንም እንኳን- ለኑሯችን ስንደክም
ዘመናችንን ብንጨርስም፣
በዓለም እርካታ የለምና- አሁንም በቃን አላልንም
ጎደሏችንን አልሞላንም፡፡
ታዲያ ለሥጋዊ ሕይወት ብቻ- እስከመቼ እንደክማልን?
ከመነንፈሳዊነት ርቀን፣
መቼስ ይሆን የምንኖረው?-በመንፈሳዊ ሕይወት
ወደ ሰማየ ሰማያት መጥቀን፡፡
መቼስ ይሆን የምንከተለው?-የአባቶቻችንን መንገድ
አገልግሎታቸውን ማን ያሳየን?
መንፈሳችንን ምን ሰለበው- ከሰማያዊት ጥሪ
ከቅዱሳን ሕብረት ማን ለየን?
የመንፈስ ልዕልናችንቀርቶ- ድክመታችንን ተመልክቶ
ዓለምስ ስለምን ይሳለቅ?
አጋንንት እንዴት ይበርታብን?-በመናፍቃን ማታለል
አማኝ እስከመቼ ይነጠቅ?
በመንፈስ ባዶ እየሆንን- እስከመቼ አንገት እንድፋ
እንዴት ዓለማውያንስ ይናቁን?
እስኪ በአባቶች ወኔ- ለጽድቅ በእውነት እንታጠቅ
ማንንነታችንን ይወቁን፡፡
እስኪ ደግሞ በዚህ ዓመት- ቃላችን በመንፈስ እናድስ
ቤተ ክርስቲያንን እናስባት፣
ፈተናዋ በዝቷልና- ልጆቿ ዓለማዊ ሆነን
መንፈሳችንም ዝሎባት፣
አጽራረ ቤተ ክርስቲያን- እንደ አሸን ፈልተዋልና
የዘመኑ ፍጻሜ ደርሶባት፡፡
እስኪ ሁላችንም ባንድ መንፈስ- ቃላችንን እናድስና
እናታችንን ደስ ይበላት፣
እኔ ግን ይሄው ለራሴ- ቃሌን እንደዚህ አድሻለሁ
የድርሻዬን ልወጣላት፡፡
ባለፀጋዋ እናቴ- አንቺ ስንዱ እመቤት ሆይ!
ሠላም ይሁን ለሁለንተናሽ፣
የፍቅርሽ ስፋት ጥልቀት- ለኔ ያደረግሽው ሁሉ
ገረመኝ እናትነትሽ፡፡
በዓለም ከወለደችኝ- ከሥጋዊቷ እናቴ
የአንቺ ፍቅር ይለያል፣
በረቀቀው ምሥጢርሽ- በግብረ መንፈስ ቅዱስ
ዳግም ልደቴን ሰጥተሽኛል፡፡
በልዩ እንክብካቤሽ- በመላዕክት ጠባቂነት
በቅዱሳንሽ ጸሎት፣
በያሬዳዊ ዜማሽ- በቅኔ በማኅሌቱ
በሰማያዊ ሥርዓት፡፡
ትህትናን በተመላ- የካህናት የሊቃውንት
የመምህራን አስተምህሮ፣
በአ-ቡ-ጊ-ዳ በአንቺው ጥበብ- በገበታ ፊደልሽ
አንደበቴ ፊደል ቆጥሮ፡፡
በውዳሴ ማርያም ዜማ- በድጓ በጾመ ድጓሽ
ከመላእክት ጋር ዘምሬ፣
ኪዳኑን አስደርሼ- ቅዳሴውን አስቀድሼ
በሥጋ ወደሙ ከብሬ፡፡
በብራና ላይ ጽሑፍሽ- በግድግዳ ላይ ሥዕልሽ
ጥበብሽን አይቻለሁ፣
በፍልፍል አብያትሽ- በረቀቁ ህንፃዎችሽ
ማንነትሽን አውቄአለሁ፣
ጠበልሽን ጠጥቼ- እምነትሽን ተቀብቼ
ተአምርሽን አድንቄአለሁ፡፡
የመጻሕፍትሽን ምሥጢር- የገድል የድርሳናቱን
የቅዱሳንን ማንነት፣
ለአንቺ ህልውና ሲሉ- የተቀበሉትን መከራ
የከፈሉትን ሰማዕትነት፡፡
የአባቶችን ልዩ ጥበብ- እንዴት ቅርሶችሽን ጠብቀው
ለእኔ እንዳደረሱልኝ፣
ትውፊትሽን ለማቆየት- አንችን ለእኔ ለማስረከብ
መስዋዕትነት ሲከፍሉልኝ፡፡
መከራ ስደታቸውን- ርሀብ ጥማታቸውን
በዓይነ ህሌናዬ አይቻለሁ፣
ፍቅር ፅናታቸው አስደንቆኝ- እነባቸውን አንብቻለሁ
ርሀባቸውን ተርቤአለሁ፡፡
እናም ይኸው እናታለም- ምንም አንቺን ለመረከብ
ማንነቴ ባይፈቅድልኝም፣
የእምነት የእውቀት ጉድለቴ- የልቤ አመንዝራነት
ባዶነቴ ቢያስጨንቀኝም፡፡
ከእኔ የአዕምሮ መርከስ- ከሐጢአት ከጉድፈቴ
የአንቺ ፍቅር ይበልጣልና፣
ይኸው ተረክቤሻለሁ፡-
የጻድቃን የሰማዕታትን- የቅዱሳን መላእክትን
ተራዳኢት አምናለሁና፡፡
እናም ከዛሬ ጀምሮ- ይኸው ቃሌን ሰጥቻለሁ
ተንበርክኬ ከእግርሽ ስር፣
ማንነትሽን ባላሳውቅ- ታሪክሽን ለዓለም ሁሉ
ያለ ፍርሃት ባልመሰክር፣
ትውፊትሽን ባላስጠበብቅ- የአምልኮና የዜማ
ሥርዓትሽን ባላስከብር፤
ምሥጢራትሽን አመሥጥሬ- ንዋያትሽን ደርድሬ
ከፍ ከፍ ባላደርግሽ፣
ልጆችሽም ይበዙ ዘንድ- ለሰማያዊ መንግሥት ጥሪ
ወንጌልሽን ባልሰብክልሽ፤
ይኸው በዳዊት መሐላ- እየማልሁ ከደጅሽ ልውደቅ፣
“ቤተ ክርስቲያን ሆይ!- ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ
ባላስብሽም ምላሴ- ከጉሮሮዬ ትጣበቅ፡፡”
No comments:
Post a Comment