(መላኩ አላምረው)
-----//-----
መለያየት አልሽው - መለያየት ዋዛ...
ቀኑ ሳይጨላልም - ይልቅ ልብ እንግዛ !
.
እኔ ልሙት ፍቅሬ - ስጋሽን ያስበላኝ
ማንም የፍቅር ደሃ - ደርሶ ስለጠላኝ
የሰዳቢውን ዘር - ከዘርሽ ገምጄ
ከከፋፋዩ ልብ - ጥላቻን ወስጄ
ንጹኋን አጋሬን - ከእርሱ ጋር ደምሬ
እኔ አንችን ልለይሽ ? - አታስቢው ፍቅሬ !
...
ተይ ! ከአፍሽ አይውጣ !
የምን መለያየት ? ቆይ ምን ስለመጣ ?
‹ኢትዮጵያዊት› ፍቅሬ - ፈጽሞ እንዳትፈሪ
ይህን ክፉ ሐሳብ ፣
እንኳንስ ለእኔ’ና - ለ’ራስሽ አታውሪ !
…
ይልቅ ስሚኝማ....
እንዳይከፋፍለን - ትንሹም ትልቁም
ለጋራ ነፃነት - ነይ በጋራ እንቁም
ነይ ሰላም እንስበክ - ነይ ፍቅር እንዝራ
የዘር ዘራዝርቱ - ፍሬ እንዳያፈራ !
.
የመለያየት ድምጽ - ጎልቶ እንዳይሰማ
ወንድም በወንድሙ - ጥይት እንዳይደማ
ወገን ከወገኑ - ቂም እንዳይቋጠር
ከዛሬው የባሰ - ሞት እንዳይፈጠር
ነይ የፍቅሬ መልአክ - ነይልኝ ሰላሜ
ነይ የምድሬ ገነት - ነይልኝ ዓለሜ
ወይ ሕይወትሽ አልፎ - ወይም ፈ’ሶ ደሜ
ሳይጫነን አፈር - ምድር ሳትበላን
ነይ እንወቅበት - በገባብን ሰይጣን
አንች’ና’ኔን ገፍቶ - ካ’ገር ሳያስወጣን
ነይ በአንድነታችን - በኅብረት ይቀጣ
በፍቅር ተቃጥሎ - ‹‹ሰባት ጮሆ›› ይውጣ !
.
እንጅ መለያየት - እንዴት ይታሰባል ?
ከማስነቀፍ አልፎ - ቃሉም ያሰድባል !
.
በምን እንለያይ ? ብሔር ዘርን ቆጥረን ?
ማነው ከማን ሚለይ ?
ሰው ከመሆን ዘር ነው - እርሱ የፈጠረን !
ጤነኛ ሕሊና - ይህንን አይከዳም
እናታችን ሔዋን - አባታችን አዳም ፡፡
...
በዓለሙ ስሌት - አሁን ያንች’ና’ኔ
ዘራችን ቢቆጠር… ይገርመኛል ለእኔ !
.
የተወለድሽ አክሱም - ያሳደገሽ ጅማ
ውልደቴ ግሽ ዓባይ ፣
እድገቴ ዓባይ ማዶ ፣ ወለጋ... ሲዳማ
አካላችን አዲስ - መንፈሳችን ዲማ !
በአባትሽ ከትግራይ - በእናትሽ ኦሮሞ
በአባቴ ከጎጃም - በአያቴ ከጋሞ
በአንዱ አያትሽ ጅማ - በሌላው ሀረሬ
በአንዱ አያቴ ባሌ - በአንደኛው ጎንደሬ
የተማርነው አዲስ - ያፋቀረን ፀባይ
ያጣመረን ፍቅር ፣
ሥጋችን ከምድር - ነፍሳችን ከሰማይ
ቆይ የምን ዘር ቆጥረን - እንዴት እንለያይ ?
…
አየሽልኝ አይደል - የዓለምን ቅሌት
ማናችን ምን ሆነን - በየትኛው ስሌት ?
‹‹እንለያይ ይሆን?›› - ብለሽ የምትፈሪው
እባክሽን ፍቅሬ ፣
ይህን ክፉ ሀሳብ - እንኳንስ ለሌላው - ለራስሽ አታውሪው፡፡
…
በትላንት ስህተቶች
በዛሬ ክስተቶች
በነገ ቅዠቶች….
ምን ልቤ ቢቆስል - ምን ልብሽ ቢደማ
መለያየት ብሎ…? - አይታሰብማ !!!
...
ቆይ አስበሽዋል ?
የፍቅር መምህራችን - ሐዲስ ዓለማየሁ
በዛብህን ልሆን - አንችን ሰብለን ያየሁ
ጥበብን የቀዳን - እኔ ከተዋነይ አንች ከበዓሉ
በየኔታ ትምህርት - ያደርን እንደቃሉ
ከቁልቢ ገብርኤል - ቁርባን ተቀብለን
ከጻድቃኔ ማርያም - ጸበል ተጠብለን
በግሸን ቃልኪዳን - በላሊበላ ጽድቅ
በአክሱማዊ ጥበብ - በሐረር ድንቃድንቅ
በአፄ ፋሲል ግቢ - በጅማ አባ ጅፋር
በኤርታሌው እሳት - ተደመ’ን በአፋር
ከዓባይ ጠጥተን - በባሮ ተራጭተን
ሐዋሳ ተዝናንተን - ሐሸንጌን ጎብኝተን
በጣና በዝዋይ - በአባያ በጫሞ
መንፈሳችን ከንፎ - ልባችን ተደ’ሞ
…
በተፈጥሮ ምሥጢር - ከአፈሯ የመጣን
ኢትጵያዊነት ! - ከወንዟ የጠጣን
ከምንጯ የቀዳን… ከሐይቅ ከኩሬዋ
ከአዝዕርቷ የበላን… ከዛፍ ከፍሬዋ…
…
ኧረ እንዴት ሲደረግ ? - እኮ ምን ሲፈጠር ?
የትኛው ሕዝባችን - በማን ሲጠረጠር ?
‹‹እንለያይ ይሆን?›› - ብለሽ የምትፈሪው
እባክሽን ውዴ !
ይሄ ክፉ ሐሳብ - ከአፍሽ እንዳይወጣ ! ለልብሽ አታውሪው !
------------------------፡፡
.....
...
-----//-----
መለያየት አልሽው - መለያየት ዋዛ...
ቀኑ ሳይጨላልም - ይልቅ ልብ እንግዛ !
.
እኔ ልሙት ፍቅሬ - ስጋሽን ያስበላኝ
ማንም የፍቅር ደሃ - ደርሶ ስለጠላኝ
የሰዳቢውን ዘር - ከዘርሽ ገምጄ
ከከፋፋዩ ልብ - ጥላቻን ወስጄ
ንጹኋን አጋሬን - ከእርሱ ጋር ደምሬ
እኔ አንችን ልለይሽ ? - አታስቢው ፍቅሬ !
...
ተይ ! ከአፍሽ አይውጣ !
የምን መለያየት ? ቆይ ምን ስለመጣ ?
‹ኢትዮጵያዊት› ፍቅሬ - ፈጽሞ እንዳትፈሪ
ይህን ክፉ ሐሳብ ፣
እንኳንስ ለእኔ’ና - ለ’ራስሽ አታውሪ !
…
ይልቅ ስሚኝማ....
እንዳይከፋፍለን - ትንሹም ትልቁም
ለጋራ ነፃነት - ነይ በጋራ እንቁም
ነይ ሰላም እንስበክ - ነይ ፍቅር እንዝራ
የዘር ዘራዝርቱ - ፍሬ እንዳያፈራ !
.
የመለያየት ድምጽ - ጎልቶ እንዳይሰማ
ወንድም በወንድሙ - ጥይት እንዳይደማ
ወገን ከወገኑ - ቂም እንዳይቋጠር
ከዛሬው የባሰ - ሞት እንዳይፈጠር
ነይ የፍቅሬ መልአክ - ነይልኝ ሰላሜ
ነይ የምድሬ ገነት - ነይልኝ ዓለሜ
ወይ ሕይወትሽ አልፎ - ወይም ፈ’ሶ ደሜ
ሳይጫነን አፈር - ምድር ሳትበላን
ነይ እንወቅበት - በገባብን ሰይጣን
አንች’ና’ኔን ገፍቶ - ካ’ገር ሳያስወጣን
ነይ በአንድነታችን - በኅብረት ይቀጣ
በፍቅር ተቃጥሎ - ‹‹ሰባት ጮሆ›› ይውጣ !
.
እንጅ መለያየት - እንዴት ይታሰባል ?
ከማስነቀፍ አልፎ - ቃሉም ያሰድባል !
.
በምን እንለያይ ? ብሔር ዘርን ቆጥረን ?
ማነው ከማን ሚለይ ?
ሰው ከመሆን ዘር ነው - እርሱ የፈጠረን !
ጤነኛ ሕሊና - ይህንን አይከዳም
እናታችን ሔዋን - አባታችን አዳም ፡፡
...
በዓለሙ ስሌት - አሁን ያንች’ና’ኔ
ዘራችን ቢቆጠር… ይገርመኛል ለእኔ !
.
የተወለድሽ አክሱም - ያሳደገሽ ጅማ
ውልደቴ ግሽ ዓባይ ፣
እድገቴ ዓባይ ማዶ ፣ ወለጋ... ሲዳማ
አካላችን አዲስ - መንፈሳችን ዲማ !
በአባትሽ ከትግራይ - በእናትሽ ኦሮሞ
በአባቴ ከጎጃም - በአያቴ ከጋሞ
በአንዱ አያትሽ ጅማ - በሌላው ሀረሬ
በአንዱ አያቴ ባሌ - በአንደኛው ጎንደሬ
የተማርነው አዲስ - ያፋቀረን ፀባይ
ያጣመረን ፍቅር ፣
ሥጋችን ከምድር - ነፍሳችን ከሰማይ
ቆይ የምን ዘር ቆጥረን - እንዴት እንለያይ ?
…
አየሽልኝ አይደል - የዓለምን ቅሌት
ማናችን ምን ሆነን - በየትኛው ስሌት ?
‹‹እንለያይ ይሆን?›› - ብለሽ የምትፈሪው
እባክሽን ፍቅሬ ፣
ይህን ክፉ ሀሳብ - እንኳንስ ለሌላው - ለራስሽ አታውሪው፡፡
…
በትላንት ስህተቶች
በዛሬ ክስተቶች
በነገ ቅዠቶች….
ምን ልቤ ቢቆስል - ምን ልብሽ ቢደማ
መለያየት ብሎ…? - አይታሰብማ !!!
...
ቆይ አስበሽዋል ?
የፍቅር መምህራችን - ሐዲስ ዓለማየሁ
በዛብህን ልሆን - አንችን ሰብለን ያየሁ
ጥበብን የቀዳን - እኔ ከተዋነይ አንች ከበዓሉ
በየኔታ ትምህርት - ያደርን እንደቃሉ
ከቁልቢ ገብርኤል - ቁርባን ተቀብለን
ከጻድቃኔ ማርያም - ጸበል ተጠብለን
በግሸን ቃልኪዳን - በላሊበላ ጽድቅ
በአክሱማዊ ጥበብ - በሐረር ድንቃድንቅ
በአፄ ፋሲል ግቢ - በጅማ አባ ጅፋር
በኤርታሌው እሳት - ተደመ’ን በአፋር
ከዓባይ ጠጥተን - በባሮ ተራጭተን
ሐዋሳ ተዝናንተን - ሐሸንጌን ጎብኝተን
በጣና በዝዋይ - በአባያ በጫሞ
መንፈሳችን ከንፎ - ልባችን ተደ’ሞ
…
በተፈጥሮ ምሥጢር - ከአፈሯ የመጣን
ኢትጵያዊነት ! - ከወንዟ የጠጣን
ከምንጯ የቀዳን… ከሐይቅ ከኩሬዋ
ከአዝዕርቷ የበላን… ከዛፍ ከፍሬዋ…
…
ኧረ እንዴት ሲደረግ ? - እኮ ምን ሲፈጠር ?
የትኛው ሕዝባችን - በማን ሲጠረጠር ?
‹‹እንለያይ ይሆን?›› - ብለሽ የምትፈሪው
እባክሽን ውዴ !
ይሄ ክፉ ሐሳብ - ከአፍሽ እንዳይወጣ ! ለልብሽ አታውሪው !
------------------------፡፡
.....
...
No comments:
Post a Comment