(መላኩ
አላምረው)
...
...
ያው
የእነርሱ እውነት
ለሌሎቹ
ሐሰት
እየሆነ
እንጂ...
ሃይማተኞችም
ፖለቲከኞችም
የሚሰብኩት
እውነት፡-
ለአንዳንዶቻችን
- ለጆሮ አይሰለችም
ያው
ለሌሎቻን ፍጹም አይመችም
‹‹እውነት
አለ የለም አሁን በዚህ መሐል ?››
ብለህ
ብትጠይቀው አንዳንዱ ያማሃል
አንዳንዱም
በድፍረት ይሳለቅብሃል !
*
* * * *
ያው
አንተም ባንተ ቤት የልብህ ውስጥ እውነት
እየሆነ
እንጂ ለሌላኛው ሐሰት
እንዳንተ
ማን ያውቃል ? እውነትን ተራቆ
ማንስ
ሚያስብ አለ ? እንዳንተ ተጨንቆ
ልቡ
እንዳንተ ሩህሩህ ይገኝ ይሆን ከሰው ?
እውነትህን
በሐሰት ሌላው እስኪከሰው…
*
* * * *
የሰው
ልጅ ምስኪን ነው ያስባል በልቡ
እውነትና
እውቀት ከውስጡ እንደገቡ
አላወቀም
እርሱ በሌላኛው ሰፈር
ሐሰተኛነቱ/ማይምነቱ
ጎልቶ እንደሚነገር
*
* * * *
በትንሽ
ሕሌና ስንመረምራት
ልክ
እንደ ሃይማኖት…
ሀገር
የጋራ ናት - ‘እውነት የግል ናት’
እውነትህን
አልነካም - እውነቴን አትንካት
ብለን
ብንደመድም
ይሄኛውም
እውነት ከቶ አይወደድም፡፡
እና
ምን ይሻላል… ?
ሰው
እውነቱን ይዞ ዝም ቢል ምን ይላል ?
....ችግሩ…
በሌላኛው
ዓለም
ዝም…
እውነት አይደለም፡፡
…..›››››››
No comments:
Post a Comment